Saturday, 15 November 2014 10:18

99 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በኬኒያ ፍርድ ቤት ተቀጡ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

          አፍሪካን ሰርቪስ ኮሚቴ ለ25 ችግረኛ እናቶች፤ እንጀራ ጋግረው መሸጥ እንዲችሉ ከጤፍ ጀምሮ የሚያስፈልጉትን ጠቅላላ ጥሬ እቃዎች በማሟላት ከትላንት በስቲያ ሾላ አካባቢ በሚገኘው ክሊኒኩ ውስጥ አስረከበ፡፡
ኤችአይቪ ቫይረስ በደማቸው ውስጥ ላለባቸው ለእነዚህ እናቶች ሁለት ኩንታል ጤፍ፣ የኤሌክትሪክ ምጣድ፣ የዱቄት ማስቀመጫ በርሜል፣ የሊጥ ማቡኪያና የውሃ ባልዲ፣ የአብሲት መጣያ ብረት ድስት፣ ጆግና ማስታጠቢያ፣ ማሰሻ ጨርቅ፣ ጎመን ዘር፣ መሶብ፣ እንቅብና የእንጀራ ማውጫ ሰፌድ በነፍስ ወከፍ ተከፋፍሏል፡፡
ተረጂዎቹ በጨረቃ ቤት፣ በዘመድ ቤትና ባስጠጓቸው በጎ ሰዎች ቤት የሚኖሩ በመሆናቸው የመጀመሪያ ወር የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያ ለእያንዳንዳቸው 300 ብርና የተረከቡትን እቃ የሚያጓጉዙበት የትራንስፖርት ወጪ ሁለት መቶ ብር ተሰጥቷቸዋል፡፡
አፍሪካዊ ስደተኞችን ለመርዳት ከ30 ዓመታት በፊት ኢትዮጵያዊ ዜግነት ባላቸው አቶ አስፈሃ ሃደራ በተባሉ ግለሰብ አሜሪካ ኒውዮርክ ውስጥ የተቋቋመው “አፍሪካን ሰርቪስ ኮሚቴ” ከ10 ዓመት በፊት ኢትዮጵያ ተከፍቶ ሥራ የጀመረ ሲሆን ክሊኒኩ የምስጢር ኤችአይቪ ምርመራ፣ የፀረኤችአይቪ (ART) ስርጭት፣ የቲቢ እንዲሁም የአባላዘር በሽታ ምርመራና ህክምና በመስጠት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያንን ሲያገለግል መቆየቱን የድርጅቱ የኢትዮጵያ ተወካይ ወይዘሪት ሃና ወ/ገብርኤል ተናግረዋል፡፡
ድርጅቱ፤ አዲስ አበባን ጨምሮ በአምስት የክልል ከተሞች በአማራ ክልል ኮምቦልቻ፣ በመቀሌ በዝዋይ እንዲሁም በሃሳዋ የጤናና የማህበረሰብ ልማት ማዕከል በማቋቋም፣ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን በተለይም እናቶችና ህፃናትን በማገልገል ላይ መሆኑን ወ/ሪት ሃና አብራርተዋል፡፡
ድርጅቱ ኤች አይቪ ቫይረስ በደማቸው ላለባቸው ህፃናት የወተትና የአልሚ ምግብ ድጋፍ የሚያደርግ ሲሆን በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ከ18 ዓመት በታች ላሉ ህፃናትና ታዳጊዎች አሜሪካ ከሚገኝ “ቶምስ ሹ” ከተባለ ድርጅት ጋር በመተባበር በዓመት ሁለት ጊዜ የጫማ  የትምህርት መሳሪያዎችና ሌሎች ድጋፎች እንደሚያደርግ ታውቋል፡፡
ከትላንት በስቲያ ችግረኛ እናቶች የገቢ ማስገኛ ስራ እንዲሰሩ ለተደረገው የጥሬ እቃና የገንዘብ ድጋፍ አገር በቀልና የውጭ ድርጅቶች ከፍተኛ ድጋፍ ማድረጋቸው የተገለፀ ሲሆን “በፔፕፋር ስሞምል ግራንት ፕሮግራም” በኩል የአሜሪካ ኤምባሲ የ30 ሺህ ዶላር ድጋፍ ማድረጉም ተጠቁሟል፡፡ እስከዛሬ ለድርጅቱ ድጋፍ ሲያደርጉ የነበሩት ቢጂአይ ኢትዮጵያ፣ ዲኬቲ ኢትዮጵያ፣ አይካፕ ኢትዮጵያ፣ ፈረንሳይ ኤምባሲ፣ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ማህበራት ኤጀንሲ እንዲሁም ድርጅቱ የሚንቀሳቀስባቸው የክልል መንግስታት የወረዳና የዞን ቢሮዎች በእለቱ ተመስግነዋል፡፡ በእለቱ የአንበሳ ማስታወቂያና የህዝብ ግንኙነት ድርጅት ባለቤትና “የትውልዱ አምባሳደር” አቶ ውብሸት ወርቅአለማሁና አርቲስት ዳንኤል ተገኝ በክብር እንግድነት ተገኝተው ስለ ድርጅቱ እንቅስቃሴ የተሰማቸውን ተናግረዋል፡፡
የጥሬ እቃ ድጋፉን የተረከቡት 18 እናቶች ሲሆኑ ቀሪዎቹ ሰባት እናቶች በሌላ ድርጅት መደገፍ አለመደገፋቸው ተጣርቶ እቃቸውን መረከብ እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡
አርቲስት ዳንኤል ተገኝና አቶ ውብሸት ወርቅአለማሁ ለገና በዓል ለተረጂዎቹ የተወሰነ ስጦታ ለማበርከት ቃል እንደገቡም ታውቋል፡፡

Read 2932 times