Saturday, 15 November 2014 10:18

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ የአመቱ ምርጥ ተባለ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ሽልማቱን ላለፉት 3 ተከታታይ አመታት ተቀብሏል
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ በያዝነው ሳምንት በአልጀርስ በተካሄደው የአፍሪካ አየር መንገዶች ማህበር 46ኛ አመታዊ ጉባኤ ላይ፣ የአመቱ የአፍሪካ ምርጥ አየር መንገድ ተብሎ መሸለሙን አስታወቀ፡፡
አየር መንገዱ ለአመቱ የአፍሪካ ምርጥ አየር መንገድ ሽልማት የበቃው በ2013 የበጀት አመት ባስመዘገባቸው ከፍተኛ ውጤቶች፣ ዘላቂነት ባለው ትርፋማነቱ እና ከሌሎች የአፍሪካ አየር መንገዶች ጋር ለመስራት በሚያስችለው አግባብነት  ያለው ስትራቴጂው እንደሆነ ገልጾ፣ ይህንን ሽልማት ላለፉት ሶስት አመታት በተከታታይነት እንዳገኘ አስታውቋል፡፡
የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረ ማርያም፣ ሽልማቱን ሲቀበሉ ባደረጉት ንግግር አየር መንገዱ ለዚህ ሽልማት በመብቃቱ ኩራት እንደሚሰማው ገልጸው፣ ለዚህ ስኬት መሰረቱ ከ8ሺህ በላይ የሚሆኑ ጠንካራ ሰራተኞቹ ትጋት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

Read 1848 times