Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Print this page
Friday, 06 January 2012 08:48

“ፕሎት ቱ ኪል ግራዚያኒ” ውይይት ይካሄድበታል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

“መገንጠያ” ነገ ይመረቃል

“ግጥምን በጃዝ” በፉጨት ታጅቦ ይቀርባል

በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተጀምሮ የጣሊያኑን ወራሪ ኃይል መሪ ማርሻል ግራዚያኒ ለመግደል የተጠነሰሱ ሴራዎች ላይ የተፈፃፈው የኢያን ካምቤል “ፕሎት ቱ ኪል ግራዝያኒ” መፅሐፍ እሁድ ከሰዓት በኋላ ስምንት ሰዓት ውይይት ይደረግበታል፡፡ ሚዩዚክ ሜይደይ ኢትዮጵያ የመፃሕፍት ንባብ እና የውይይት መርሃ ግብር ያሰናዳውን ውይይት አምስት ኪሎ በሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተመዘክር በመገኘት መነሻ ሀሳብ አቅርበው የሚመሩት የታሪክ ተመራማሪ አቶ ብርሃኑ ደቦጭ ናቸው፡፡

ይህ በዚህ እንዳለ የኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር አባል የሆኑት አቶ አረጋዊ ደጀኔ የፃፉት “መገንጠያ” የግጥም መፅሐፍ ነገ ይመረቃል፡፡ “መገንጠያ” የሚመረቀው በሐገር ፍቅር ትያትር ቤት ከጧቱ አራት ሰዓት ነው፡፡በሌላም በኩል “ግጥምን በጃዝ” ኪነጥበባዊ ዝግጅት በመጪው ረቡዕ ከምሽቱ 12 ሰዓት በዋቢሸበሌ ሆቴል ይቀርባል፡፡ 50 ብር የመግቢያ ዋጋ በሚጠየቅበት ዝግጅት የአብርሃም ወልደገብርኤል ግጥም በፉጨት ታጅቦ የሚቀርብ ሲሆን ከዚህም ሌላ አርቲስት ታምሩ ብርሃኑ አጭር ድራማ፤ አርቲስት ግሩም ዘነበ መነባንብ እንዲሁም ሜሮን ጌትነት፣ ኤፍሬም ስዩም፣ ምሥራቅ ተረፈ፣ እና ሌሎችም የግጥም ሥራዎቻቸውን ያቀርቡበታል፡፡

 

 

 

Read 1770 times Last modified on Friday, 06 January 2012 09:25

Latest from