Saturday, 25 October 2014 10:29

ዋረን ቡፌት በ2 ቀናት ውስጥ 2 ቢ. ዶላር ከሰሩ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

አሜሪካዊው ቢሊየነር ዋረን ቡፌት 400 ሚሊዮን የአክሲዮን ድርሻ የያዙበትንና ከታላላቅ የኢንቨስትመን መስኮቻቸው አንዱ የሆነውን የኮኮካ ኮላ ኩባንያ ጨምሮ፣ በተለያዩ ኩባንያዎቻቸው በደረሰባቸው ኪሳራ በ2 ቀናት ውስጥ 2 ቢ. ዶላር ማጣታቸውን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡ ባለፈው ሰኞ የተከሰተው የ7 በመቶ የአክሲዮን ዋጋ ማሽቆልቆል፣ አይቢኤም ቴክ30 የተባለውን ኩባንያቸውን 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ያሳጣቸው ባለጸጋው ቡፌት፤  በነጋታው ደግሞ ኮካኮላ ኩባንያ ካቀደው ዕለታዊ ገቢ 6 በመቶ ቅናሽ በማሳየቱ 1 ቢሊዮን ዶላር አጥተዋል፡፡አመቱ ለቡፌት የኪሳራ ነበር ያለው ዘገባው፤ ቴስኮ የተባለው ኩባንያቸው አመታዊ ትርፍ 47 በመቶ ቅናሽ ማሳየቱን አስታውሷል፡፡
የአክሲዮን ገበያ ዋጋ እያሽቆለቆለ ቢመጣም ታዲያ፣ ዋረን ቡፌት ግን የአክሲዮን ድርሻ መግዛታቸውን እንደቀጠሉ በሰጡት መግለጫ  ማስታወቃቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡

Read 2844 times