Monday, 13 October 2014 07:39

“አፈር ብላ” የግጥም መድበል ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በዳንኤል ቢሰጥ እቴቴ የተፃፉ ግጥሞች የተካተቱበት “አፈር ብላ” የተሰኘ የግጥም መድበል፤ ሰሞኑን ገበያ ላይ ውሏል፡፡ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ሽሙጦችና ፍልስፍና ነክ ግጥሞች እንዲሁም አገራዊ ፉከራና ሽለላ ቀመስ ግጥሞች የተካተቱበት መፅሃፉ፤ ፈገግና ዘና የሚያደርጉ ርእሰ ጉዳዮችንም ይዳስሳል፡፡
በ100 ገፆች ተቀንብቦ የተዘጋጀው “አፈር ብላ” የግጥም መድበል፤ በ25 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ መፅሃፉ የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ በሩሲያ የሳይንስና የባህል ማዕከል (ፑሽኪን አዳራሽ) ይመረቃል ተብሏል፡፡

Read 2920 times