Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 31 December 2011 12:05

የክቡር ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ ተቋም ተመሰረተ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በታዋቂው ደራሲ በክቡር ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ ስም የተሰየመው የቋንቋ፣ የባህል፣ የታሪክና የምርምር ተቋም ሰሞኑን ተመሰረተ፡፡ በጐጃም ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ስር የተቋቋመው የክቡር ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁ የቋንቋ፣ የባህል፣ የታሪክና የምርምር ተቋም በሙዚቃ፣ በቲያትር፣ በስነ ፅሁፍ፣ በስዕልና ቅርፃ ቅርፅ፣ በፊልም፣ በባህልና በታሪክ ዘርፎች የተለያዩ ስራዎችን ያከናውናል፡፡ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ቴዎድሮስ በካፋ በምስረታ ስነ ስርአቱ ላይ እንደተናገሩት፤ ተቋሙ በተለያዩ የኪነጥበብና የባህል ነክ ጉዳዮች ላይ የማሰልጠኛ ማንዋሎችን በማዘጋጀት ስልጠና የመስጠት፣ ምርጥ የፈጠራ ስራዎች ለህትመት የሚበቁበትን መንገድ የማመቻቸት፣ በኪነጥበባትና በባህል ዙሪያ ጥልቀት ያላቸው ጥናትና ምርምሮችን የማካሄድ ሥራዎችን በመስራት የጥበብ ሃብት ለትውልድ እንዲተላለፍ የማድረግ አላማ አለው፡፡ የክቡር ዶ/ር ሀዲስ አለማየሁን ተቋም ለመመስረት ባለፈው ሰሞን በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በተከናወነው አውደ ጥናት ላይ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት የተውጣጡ ተወካዮች የተለያዩ ጥናታዊ ፅሁፎችን አቅርበው በተቋሙ አደረጃጀትና አሰራር ረቂቅ ማኑዋል ላይም ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡

 

 

 

Read 4221 times Last modified on Saturday, 31 December 2011 12:09