Monday, 06 October 2014 07:28

300 ያህል የአውሮፓ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስት እያደረጉ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

          በአሁን ወቅት ወደ 300 የሚሆኑ የአውሮፓ ኩባንዎች በኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች የተሰማሩ ሲሆን የአውሮፓ ኩባንያዎችን ይበልይ ወደ ሃገር ውስጥ ለመሳብ ጥረት እተደረገ ነው ተብሏል፡፡ “የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንትና ቢዝነስ ማነቃት በሚል መርህ በአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያ ልኡክ እና በህብረቱ የቢዝነስ ዶርም አዘጋጅነት በአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል በትናንትናው እለት ኢግዚብሽንና ኮንፈረንስ የተካሄደ ሲሆን በሃገሪቱ ተፈትሸዋል፡፡
የኮንፍረንሱ ዋነኛ አላማ አውሮፓ ህብረት እና የኢትዮጵያ የቢዝነስ ባለድርሻ አካላት በኢትዮጵያ ስላለው የቢዝነስ እና ኢንቨስትመንት አማራጭ እና ለችግሮቹ መፍትሄ በሚሆኑ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት የነበረ ሲሆን በእለቱም የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ተገኝተዋል፡፡ በኮንፈረንሱ ላይም በሃገሪቱ ለአውሮፓ ባለሃብቶች ተግዳሮት ናቸው በተባሉት ታክስ፣ ንግድ ፍቃድ፣ ግብር እና የውጭ ምንዛሬ ጉዳይ ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል በእለቱ ኢትዮጵያ የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ በምታደርገው ጥረት ላይ ሰፊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ከንግድ ፍቃድ ጋር ተያይዞ ይውጭ ባለሃብቶች የሚያጋጥማቸው ተግዳሮቶች በስፋት ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

Read 1828 times