Monday, 29 September 2014 09:51

“ያንዳንድ አጥንት እጣ” የግጥም መድበል ገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በመምህር ሃይማኖት ታደሰ አራጋው የተፃፈው “ያንዳንድ አጥንት እጣ” የተሰኘ የግጥም መድበል በገበያ ላይ ዋለ፡፡ በመፅሃፉ ውስጥ ተካተቱት ግጥሞች ማህበራዊና ፖለቲካዊ እንዲሁም ፍልስፍናዊ ጉዳዮችን ያነሳሉ ተብሏል፡፡ 43 ግጥሞችን የያዘው መድበሉ፤ 48 ገፆች ያሉት ሲሆን በ20 ብር እየተሸጠ እንደሆነ ታውቋል፡፡
ደራሲው ከዚህ ቀደም “እንበለ ጥበብ” እና “የማርገዝ ነፃነት” የተሰኙ የግጥም መፅሃፍት ያሳተመ ሲሆን ከሌሎች ገጣሚያን ጋር በመሆንም “የማለዳ ነፍሶች” የተሰኘ የግጥም መድበል ለአንባቢያን አድርሷል፡፡

Read 2117 times