Saturday, 20 September 2014 11:50

“ስውር ስፌት ቁ.2” ተመረቀ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

በጋዜጠኛ፣ ገጣሚና ተርጓሚ ነቢይ መኰንን የተጻፈው “ስውር ስፌት ቁ.2” የግጥም መድብል ትናንት ምሽት
በዋቢ ሸበሌ ሆቴል አዳራሽ ተመረቀ፡፡የኪነጥበብ ቤተሰቦችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት
በተከናወነው የምረቃ ስነ ስርዓት ላይ፣ ገጣሚውን ጨምሮ አንጋፋና ወጣት ገጣሚያን ስራዎቻቸውን ለታዳሚው
አቅርበዋል፡፡
ገጣሚ ነቢይ በመኰንን ከዚህ በፊት “ጥቁር፣ ነጭ ግራጫ ግጥሞች” እና “ስውር ስፌት ቁ.1” የግጥም መፃህፍት
ለአንባቢ ያበረከተ ሲሆን፣ በታዋቂዋ አሜሪካዊት ደራሲ ማርጋሬት ሚሼል የተጻፈውን “Gone With The
Wind” የተሰኘ ተወዳጅ የረጅም ልቦለድ መጽሃፍ፣ “ነገም ሌላ ቀን ነው” በሚል ርዕስ ወደ አማርኛ ተርጉሞ
በማቅረብ ይታወቃል፡፡
“ስውር ስፌት ቁ.2” በመጽሃፍት መደብሮችና በአዟሪዎች እየተሸጠ ይገኛል፡፡

Read 3147 times Last modified on Monday, 22 September 2014 14:14