Saturday, 20 September 2014 10:20

የውቤ በረሃ የልማት ተነሺዎች ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ቅሬታ ማቅረባቸውን ገለፁ

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(3 votes)

            የአዲስ አበባ አስተዳደርና ወረዳው በአካባቢያችን የመልሶ ማልማት ስራ የገባልንን ቃል አልጠበቀም የሚሉት በአራዳ ክ/ከተማ የውቤ በረሃ የልማት ተነሺዎች፣ ቅሬታቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤትና ለከተማ ልማት ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ማቅረባቸውን ጠቁመው ከባለስልጣናቱ በጐ ምላሽ እንደሚጠብቁ ለአዲስ አድማስ ገለፁ፡፡ የከተማ አስተዳደሩ እና የወረዳው ፅ/ቤት ኃላፊዎች ከአንድ አመት በፊት ከቦታቸው ሲነሱ በከተማው መሃል ባሉ የኮንዶሚኒየም ሳይቶች መኖሪያ ቤት ይሠጣችኋል የሚል ቃል እንደገባላቸው የገለፁት ከ217 በላይ የሚሆኑ የአካባቢው አባወራዎች፤ ሃላፊዎች የገቡትን ቃል አጥፈው ቃል ታጥፎ ገላን ሳይት ትሄዳላችሁ ተገቢ አይደለም ብለዋል፡፡ ባለፈው እሁድ ከአራዳ ክ/ከተማ የስራ ሃላፊዎች ጋር ባደረጉት ስብሰባም ለተነሺዎቹ የተዘጋጀው የገላን ሳይት ነው በሚል ውሳኔው እንደማይቀየር የሚገልፅ ምላሽ ማግኘታቸውን፤ የጠቀሱት የልማት ተነሺዎቹ ኮሚቴ አባላት፤ ጉዳዩን በዝርዝር የሚያስረዳ የቅሬታ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤትና ለከተማ ልማት ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር አስገብተው ምላሹን እየተጠባበቁ እንዳሚገኙ ገልፀዋል፡፡

Read 1879 times