Saturday, 06 September 2014 11:40

“ኪነጥበብ የሰላም እርግብ ናት” የኪነ-ጥበብ ጉዞ ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

         በአብርሃም ግዛው ኢንተርቴይመንትና የፕሬስ ስራዎች እና በሰለሞን ማርያ ፊልም ፕሮዳክሽን ትብብር የተጠነሰሰው “ኪነጥበብ የሰላም እርግብ ናት” የተሰኘ በዘጠኙም ክልሎች በየተራ የሚዘጋጅ ፕሮግራም ሊካሄድ እንደሆነ ተገለፀ፡፡ አዘጋጆቹ እንዳሉት፤ የዝግጅቱ ዓላማ የኢትዮጵያን ሰላም ወዳድነት፣ ስላሉን የቱሪስት መስህቦች፣ ስለመቻቻል ባህላችንና ስለተፈጥሮ እሴቶቻችን ለትውልደ ኢትዮጵያዊያንና ለመላው ዓለም ማስተዋወቅ ነው፡፡
በመስቀል ዋዜማ የዳመራ እለት በአዲስ አበባ የሚጀመረው ይሄው ፕሮግራም፤ በብሄር ብሄረሰቦች ሙዚቃ፣ በስዕል አውደርዕይ፣ በመድረክ ተውኔትና በተለያዩ ባህላዊ ትዕይንቶች፣ የሰላም አምባሳደር ምትሆን ቆንጆ የምትመረጥበት የቁንጅና ውድድር እንዲሁም በአስጐብኚዎች አውደርዕይ ይታጀባል ተብሏል፡፡ ዝግጅቱ ከአዲስ አበባ በመቀጠል  አዳማ፣ ሃዋሳ፣ ድሬደዋ,ኧ ባህርዳርና መቀሌ የሚካሄድ ሲሆን በቀጣይ በሌሎችም ክፍሎች እንደሚካሄድ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 1982 times