Saturday, 30 August 2014 11:25

“ከልካይ የሌለው ስጥ” መፅሀፍ ሰኞ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ጋዜጠኛ፣ ደራሲና ዓለም አቀፍ የሰላም አምባሳደር በሆነው ወጣት መኮንን ሞገሴ የተዘጋጀው “ከልካይ የሌለው ስጥ” የተሰኘ መፅሀፍ የፊታችን ሰኞ በብሄራዊ ቴአትር ይመረቃል፡፡ መፅሀፉ በዩኒቨርሲቲ ሴት ተማሪዎች የስነ-ልቦና ዝቅጠት ላይ ያተኩራል የተባለ ሲሆን ፀሐፊው በስድስት ወራት የመስክ ቆይታው በአዲስ አበባ፣ ሃዋሳ፣ ዲላ፣ ሐገረ-ማርያም፣ ያቤሎ፣ ኢትዮጵያ ሞያሌ፣ ኬኒያ ሞያሌ እና ኬንያ ጋንቦ ድረስ በመሄድ በጎዳና ተዳዳሪነት፣ በተሸካሚነት እንዲሁም በአስተናጋጅነት እየሰራ የታዘባቸውን የከተበበት እንደሆነ ታውቋል፡፡ በእሁል ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን አስተባባሪነት የሚመረቀው መፅሀፉ፤ የደራሲው ሁለተኛ ስራ ሲሆን ከዚህ ቀደም “የአስተናጋጁ ገፆች ቅፅ 1” የተሰኘ መፅሀፍ ለንባብ ማብቃቱ ታውቋል፡፡

Read 2803 times