በወጣት ገጣምያን የተጠነሰሰው “ግጥምን በጃዝ” ባለፈው ረቡዕ ምሽት የ3ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን በብሄራዊ ቴአትር አዳራሽ በተለያዩ የጥበብ ዝግጅቶች አከበረ፡፡ በክብረ በዓሉ ምሽት ግጥሞች፣ ሙዚቃዊ ተውኔት፣ዲስኩሮችና የእውቅና የሽልማት ስነስርአቶች ተካሂደዋል፡፡
በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ተጀምሮ ወደ ራስ ሆቴል የተዛወረው “ግጥምን በጃዝ”፤ በኪነ-ጥበብ አፍቃሪያን ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈ ፕሮግራም ነው፡፡ በምሽቱ የጥበብ ዝግጅት ላይ ጸሀፌ ተውኔትና ገጣሚ ጌትነት እንየው፣ ገጣሚ ነቢይ መኮንን፣ አርቲስት ግሩም ዘነበ፣ ገጣሚ አበባው መላኩ፣ ምህረት ደበበ፣ በረከት በላይነህ፣ ምስራቅ ተረፈና ሌሎችም የጥበብ ስራዎቻቸውን ለታዳሚው ያቀረቡ ሲሆን አዳራሹ ገና በጊዜ ጢም ብሎ ሞልቶ ነበር፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና