Print this page
Saturday, 23 August 2014 11:43

በአሜሪካ አንድ ልጅ ለማሳደግ ከግማሽ ሚ. ዶላር በላይ ወጪ ይደረጋል

Written by 
Rate this item
(4 votes)

ወጪው የኮሌጅ ክፍያን አያካትትም

በአሜሪካ ወላጆች አንድን ልጅ ከተወለደበት ጊዜ አንስቶ 18 አመት እስኪሞላው ድረስ በወጉ ተንከባክቦ ለማሳደግ የኮሌጅ ክፍያን ሳይጨምር ግማሽ ሚሊዮን  ዶላር ያህል ወጪ እንደሚጠይቃቸው ሲኤንኤን ዘገበ፡፡
አሜሪካውያን ወላጆች አንድን ልጅ ለማሳደግ ወጪ የሚያደርጉት ገንዘብ እንደገቢያቸው መጠን የሚለያይ መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፤ አነስተኛ ገቢ ያላቸው የአገሪቱ ወላጆች ከ145 ሺህ በላይ፣ መካከለኛ ገቢ ያላቸው ከ245 ሺህ በላይ፣ ከፍተኛ ገቢ ያላቸው ደግሞ 455 ሺህ ያህል ዶላር ወጪ እንደሚያደርጉ ገልጿል፡፡
ወጪዎቹ የተሰሉት ወላጆች ለቤት፣ ለምግብ፣ ለትራንስፖርት፣ ለአልባሳት፣ ለጤና፣ ለትምህርትና ለሌሎች ጥቃቅን ጉዳዮች የሚከፈሉ ገንዘቦችን መሰረት በማድረግ ሲሆን ባለፉት አመታት ለጤናና ለልጆች እንክብካቤ የሚወጣው ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን ዘገባው አስረድቷል፡፡
በአገሪቱ እየናረ የመጣው የትራንስፖርትና የምግብ ዋጋ ለአሜሪካውያን ወላጆች ከፍተኛ ጫና እየፈጠረ እንደሚገኝ የጠቆመው ዘገባው፤ ባለፉት አስር አመታት የነዳጅ ዋጋ በእጥፍ መጨመሩንና የምግብ ዋጋም ባለፉት ስድስት አመታት ከ13 በመቶ በላይ ጭማሪ ማሳየቱን አመልክቷል፡፡

Read 2644 times
Administrator

Latest from Administrator