Print this page
Saturday, 23 August 2014 11:40

ኢራናዊቷ ተመራማሪ አለማቀፉን የሂሳብ ሜዳልያ ተቀበለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ኢራናዊቷ የሂሳብ ባለሙያ ፕሮፌሰር ሜርያም ሚርዛካኒ፤ አለማቀፉ የሂሳብ ህብረት የሚሰጠውንና ከኖቤል ሽልማት ጋር የሚስተካከለውን የፊልድስ ሜዳል ሽልማት መቀበሏን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
በየአራት አመቱ በአለማቀፍ ደረጃ የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የሂሳብ ተመራማሪዎች የሚሰጠውን ይህን ሽልማት በመውሰድ የመጀመሪያዋ የሆነችው ፕሮፌሰር ሚርዛካኒ፤ ትኩረቷን በጂኦሜትሪ ላይ በማድረግ፣ ሬማን ሰርፌስስ ከተባሉ ቅርጾች ጋር የተያያዘና ውስብስብ ሂሳባዊ ቀመር የሚጠይቅ የምርምር ውጤት ይፋ በማድረጓ ለሽልማት እንደበቃች ዘገባው ገልጿል፡፡
የአንደኛና የሁለተኛ እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርቷን በቴህራን የተከታተለችው ሚርዛካኒ፤ ወደ አሜሪካ በማቅናት የፒኤችዲ ትምህርቷን በሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የተከታተለች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅትም ካሊፎርኒያ በሚገኘው ስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነትና በተመራማሪነት እየሰራች ትገኛለች፡፡ 

Read 1530 times
Administrator

Latest from Administrator