Saturday, 16 August 2014 11:04

“የሰቆቃው ዘመን በታጋይ ህይወት ውስጥ” ለንባብ በቃ፤

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በአቶ ተክሉ አብርሃ በእንግሊዝኛ ተፅፎ፣ በመምህርና ጋዜጠኛ ግርማይ ገ/ፃዲቅ ወደ አማርኛ የተመለሰው “የሰቆቃው ዘመን በታጋይ ህይወት ውስጥ” የተሰኘው በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ መፅሀፍ ሰሞኑን ለንባብ በቅቷል፡፡
መፅሀፉ የደርግን ዘመን አስከፊነት፣ በፊውዳሉ ስርዓት ኢትዮጵያ ምን ያህል ኋላቀርነት ጠናውቷት እንደነበር፣ ስለ ኢህአፓና ሌሎች የወቅቱ ሁነቶች ላይ ትኩረት አድርጓል፡፡ በ23 ምዕራፎች ተከፋፍሎ በ376 ገፆች የቀረበው መፅሀፉ፤ ለአገር ውስጥ በ100 ብር፣ ለውጭ አገር በ20 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡
በሌላ በኩል፣ “መስፍን ኃብተማሪያም፣ ህይወቱና ስራዎቹ” በሚል ርዕስ ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ በነገው እለት ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በብሄራዊ ቤተመፃህፍትና ቤተመዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት እንደሚያካሂድ አስታወቀ፡፡
በዕለቱ የደራሲው ስራዎች የሚዳሰሱ ሲሆን የውይይት መነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት ደራሲና ሃያሲ አቶ አለማየሁ ገላጋይ እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 1225 times