በናትናኤል ፋንቱ የተፃፈው “ከነፍስ እስከ ዩኒቨርስ” የተሰኘ መፅሀፍ ባለፈው ሳምንት ለንባብ በቅቷል፡፡ መፅሀፉ በዋናነት በስነ ፈለክ ምርምር፣ በፕላኔቶች፣ በፀሐይና መሰል ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው፡፡ “ከነፍስ እስከ ዩኒቨርስ” ስለምንኖርባት ዓለም ምን ያህል እናውቃለን፣ ማወቁስ ለምን አስፈለገ? ስለክዋክብት ማወቅስ ምን ይጠቅማል ለሚሉትና ተያያዥ ጥያቄዎች መጠነኛ መልስ ይሰጣል ተብሏል፡፡ በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች የተከፈለው መፅሀፉ፤ 156 ገፆች ያሉት ሲሆን በ40 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ የመፅሀፉ አዘጋጅ ናትናኤል ፋንቱ ከዚህ ቀደም “የእኔ ስላሴዎች - ህይወት፣ ፍቅርና ሳቅ”፣ “ስለ አረንጓዴ አይኖች”፣ “ሴቶች ለምንድን ነው ወሬ የማያቆሙት?” እና “የአምላክነት ቅምሻ” የተሰኙ መፃህፍትን ማሳተሙ ይታወሳል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና