Saturday, 09 August 2014 11:48

“ሰልፍ ሜዳ” የተሰኘ ልብወለድ መፅሀፍ ገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በቀድው የ“አዲስ ነገር” ጋዜጣ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ግርማ ተስፋው የተደረሰው “ሰልፍ ሜዳ” የተሰኘ ልብወለድ መፅሀፍ ሰሞኑን ለንባብ በቅቷል፡፡ የልቦለዱ ማጠንጠኛ ከአብዮት በኋላ በሚያጋጥም የህይወት ፈተና ላይ በተዋቀረ በተለይም የሰው ልጆች በአብዮት ማግስት ለሚኖሩት ህይወት ትርጉም ማጣት፣ ብቸኝነት፣ ድብታና የባዶነት አዘቅት ውስጥ መስጠም በመፅሀፉ እንደ ዋንኛ ጭብጥ ተነስቷል፡፡
240 ገፆች ያሉት ልቦለዱ፤ በሊትማን መፃህፍት አከፋፋይነት የቀረበ ሲሆን በ49 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ደራሲው ከዚህ ቀደም “የጠፋችውን ከተማ ሐሰሳ” የተሰኘ የግጥም መድበል ለንባብ ማብቃቱ ይታወሳል፡፡

Read 3513 times