የጋዜጠኛ ግርማ ወ/ማርያም “የ ‘ኛ ነገር” የተሰኘ የግጥም መድበል ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ ማህበራዊ ትዝብቶች፣ ፖለቲካዊ ጉዳዮችና ሌሎች ርዕሶች የተዳሰሱበት የግጥም መፅሀፉ፤ 76 ግጥሞችን ያካተተ ሲሆን በ70 ገፆች የተቀነበበ ነው፡፡ መፅሀፉ ድንገት ከቤቱ እንደወጣ ለቀረውና በጣም ለሚያከብረው ደራሲ በዓሉ ግርማ መታሰቢያነት ይሁንልኝ ብሏል፡፡ መድበሉ በ25 ብር ይሸጣል፡፡ ጋዜጠኛው ከዚህ በፊት “አለቃ ሙስና እና…” በሚል ርዕስ መፅሃፍ አሳትሟል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና