የመካከለኛው ምስራቅ አገራት ኩባንዎች በኢትዮጵያ ከ21 ቢሊዮን ብር በላይ የሚያንቀሳቅሱ የተለያዩ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች እንዳላቸው ወርልድ ቡሊቲን ዘገበ፡፡
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ ያወጣውን መረጃ በመጥቀስ ዘገባው እንዳለው፣ ኩባንያዎቹ በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች 179 ያህል የምርት፣ የግብርና፣ የሪል እስቴትና የማሽነሪ ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን እያንቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡ 80 የሚደርሱ ፕሮጀክቶች የአገሪቱ መንግስት ትኩረት በሰጠው የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ውስጥ እንደሚገኙ ሲታወቅ 35 ያህሉ ደግሞ ለዘርፉ ግብዓት በሚያመነጨው የግብርናው ዘርፍ እንደተካተቱ ዘገባው አመልክቷል፡፡
በኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች ከተሰማሩት የመካከለኛው ምስራቅ አገራት ቀዳሚውን ስፍራ የምትይዘው ሳኡዲ አረቢያ ስትሆን አገሪቱ በኢትዮጵያ 86 ፕሮጀክቶችን እያከናወነች እንደምትገኝ ዘገባው ጠቁሞ፤ ከመካከለኛው ምስራቅ አገራት በተጨማሪ ሱዳን፣ ግብጽ፣ ደቡብ አፍሪካና ናይጀሪያን የመሳሰሉ የአፍሪካ አገራትም በተለያዩ ኢንቨስትመንቶች ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ አመልክቷል፡፡
Saturday, 09 August 2014 11:15
የመካከለኛው ምስራቅ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ከ21 ቢ. ብር በላይ ያንቀሳቅሳሉ
Written by Administrator
Published in
ዜና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል