Saturday, 02 August 2014 12:01

ህፃናት ለእግዚአብሔር የፃፏቸው ደብዳቤዎች

Written by 
Rate this item
(13 votes)

ውድ እግዚአብሔር፡-
እንስሳትም ግንኙነታቸው ከአንተ ጋር ነው ወይስ የራሳቸው እግዚአብሔር ሰጥተሃቸዋል?
ናንሲ፤ የ5 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
እግዚአብሔር መሆንህን እንዴት አወቅህ?
ሳሚ፤ የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
የተለያዩ ሃይማኖቶች መፍጠርህ ደስ ይላል፡፡ አንዳንዴ ግን አይደባለቅብህም?
አርኖልድ፤ የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
ህፃናቶች ከየት ነው የሚመጡት? ማሚ ሆድ ውስጥ ማን ነው የሚከታቸው? ከዚያ በፊት አንተ ጋ ነው የሚኖሩት? ሁሉንም መልስልኝ እሺ፡፡ እወድሃለሁ፡፡
ሱዛን፤ የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
አዳዲስ እንስሳት መፍጠር የተውከው ለምንድን ነው? እኛ  እኮ የድሮ እንስሳት ብቻ ነው ያሉን፡፡
ጆኒ፤ የ5 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
ወንድሜ ሁሌ አይጥ ነኝ እያለ ይቀልዳል፡፡ ለምን ጅራት አትሰጠውም?
ጆዲት፤ የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
ማታ ማታ ኮከቦቹን በትክክል ስለምትደረድራቸው ታስደስተኛለህ፡፡
ጄፍ፤ የ5 ዓመት ህፃን  

Read 2096 times