Saturday, 02 August 2014 10:57

የጋዜጠኛ ተመስገን ጉዳይ ለመጪው ዓመት ተቀጠረ

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(8 votes)

       በቀድሞው የ“ፍትህ” ጋዜጣ ላይ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ሲሰራ ሶስት ክሶች የቀረቡበት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ በተደጋጋሚ ቀጠሮው ሲተላለፍበት ቆይቶ፣ ከትላንት በስቲያ ለመጪው ዓመት ተቀጠረ፡፡ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት፣ ሐምሌ 11 ቀን 2006 ዓ.ም ጋዜጠኛው የቀረቡበት ሶስት ክሶች ላይ ማስረጃዎችን መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ሲጠበቅ፣ዳኛው አዲስ ናቸው በሚል ተለዋጭ ቀጠሮ ለሐምሌ 24 መሰጠቱ ይታወሳል፡፡ ከትናንት በስቲያ ሃሙስ ከሰአት በኋላም በድጋሚ ዳኛው በመቀየራቸው መዝገቡን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ በጋዜጠኛው ላይ የቀረቡት ሶስት ክሶች በቀድሞው “ፍትህ” ጋዜጣ ላይ “መጅሊሱ፣ ሲኖዶሱና የአብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ማጥመቂያዎች”፣ “የፈራ ይመለስ” እና “የብሄረሰቦች መብት እስከ መጨፈር” በሚሉ ርእሶች በተለያዩ ጊዜያት በወጡት ፅሁፎች፤ መንግስትን በአመፅ ለመናድ ቀስቅሷል፣ የመንግስትን ስም አጥፍቷል፣ የህዝብን አስተሳሰብ ለማናወጥ ሰርቷል፤ የሚሉ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ የፍ/ቤት የክርክር ሂደቱ ሁለት አመታትን መፍጀቱ ታውቋል፡፡

Read 2893 times