Print this page
Saturday, 02 August 2014 10:48

ክትፎ በአሜሪካ ከ100 የአመቱ ተወዳጅ ምግቦች አንዱ ሆነ

Written by 
Rate this item
(6 votes)

           በአሜሪካ ዳላስ አካባቢ ከፍተኛ ተወዳጅነት ካላቸውና የተለያዩ አገር ዜጎች አዘውትረው ከሚመገቧቸው የአመቱ 100 ምርጥ የምግብ አይነቶች ውስጥ፣ ክትፎ አንዱ መሆኑን ዳላስ ኦብዘርቨር ድረገጽ ዘገበ፡፡ ዳላስ ኦብዘርቨር በተለያዩ ሬስቶራንቶች በመዘዋወር የሰራውን ጥናት በመጥቀስ፣ከትናንት በስቲያ በድረ-ገጹ እንዳስነበበው፣ ዳላስ ውስጥ በሚገኘው ሼባ የተሰኘ የኢትዮጵያውያን ሬስቶራንት ውስጥ እየተዘጋጀ የሚቀርበው ክትፎ፣ በአመቱ የዳላስ አካባቢ ተወዳጅ 100 የምግብ አይነቶች ዝርዝር ውስጥ የ50ኛ ደረጃን ይዟል፡፡ ከሁሉም የምግብ አይነቶች በቀዳሚነት የተቀመጠው ኦይስተር ተብሎ የሚጠራው የባህር ውስጥ ምግብ ሲሆን፣ በተከታይነት የተቀመጠው ደግሞ፣ በባህላዊ አሰራር የሚዘጋጀው የቱርኮች ሳንዱች ነው፡፡

ቺክን ሺሽ ከባብ የተባለው ከዶሮ ስጋ የሚሰራ ምግብ በሶስተኛነት ተቀምጧል፡፡ ዝርዝሩ በዳላስ አካባቢ የሚኖሩ የስጋም ሆነ የአትክልት ተመጋቢዎች በአመቱ የበለጠ የተመገቧቸውንና ያዘወተሯቸውን የተለያዩ የዓለም አገራት የምግብ አይነቶች የያዘ ሲሆን፣ በዝርዝሩ ውስጥ የተካተቱት ምግቦች የሚገኙባቸውን ሬስቶራንቶች፣ አሰራራቸውን፣ የተለዩ የሚያደርጓቸውን መገለጫዎች ወዘተ ጠቁሟል፡፡ በዘንድሮው የዳላስ ተወዳጅ የምግብ አይነቶች ዝርዝር ውስጥ ከስጋ፣ ከእንቁላል፣ ከአትክልትና ከመሳሰሉት ምግቦች የተካተቱ ሲሆን፣ የአሳና የፓስታ ምግቦችም ተጠቅሰዋል፡፡ የሳንዱችና የበርገር አይነቶችም ከአመቱ ተወዳጅ ምግቦች ተርታ ተሰልፈዋል፡፡

Read 6058 times
Administrator

Latest from Administrator