የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ከ612 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ከአላማጣ - መሆኒ - መቀሌ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ሃይል ማስተላለፊያ መስመር ሠርቶ አጠናቀቀ፡፡ በየካቲት 2004 ዓ.ም ስራው የተጀመረው የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር፤ 141 ኪሎ ሜትር የሚረዝም ሲሆን 230 ኪሎ ቮልት ኤሌክትሪክ ይሸከማል፡፡
ሙሉ ለሙሉ ስራው የተጠናቀቀው ይህ ፕሮጀክት፤ ከተከዜ ሃይል ማመንጫ 300 ሜጋ ዋት፣ ከአሽጐዳ ንፋስ ሃይል ማመንጫ 120 ሜጋ ዋት የሚመነጨውን የኤሌክትሪክ ሃይል ያስተላልፋል፡፡
በአምስት አመቱ እድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድና ትግበራ በአጠቃላይ 10ሺህ ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ለማመንጨት መታቀዱን የጠቆመው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ኮርፖሬሽን፤ የህዳሴው ግድብ ከ35 በመቶ በላይ፣ የጊቤ 3 ግድብ ከ86 በመቶ በላይ፣ የገናሌ ዳዋ ከ56 በመቶ በላይ ግንባታቸው መጠናቀቁን ገልጿል፡፡
Published in
ዜና