Wednesday, 30 July 2014 07:52

“የእምነት ወጎች” የግጥም ስብስብ ሲዲ ለገበያ ቀረበ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

በገጣሚ ትዕግስት ማሞ የተሰናዳው “የእምነት ወጎች” የተሰኘ የግጥም ስብስብ በሲዲ ተዘጋጅቶ ለገበያ የቀረበ ሲሆን ባለፈው ረቡዕ ምሽት በዋቢ ሸበሌ ሆቴል በድምቀት ተመርቋል፡፡
16 ግጥሞችን ያካተተው የግጥም ሲዲ በተመረቀበት ወቅት የቀድሞ መምህሯ ረዳት ፕ/ር ሙሉጌታ ጀዋሬ፣ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራና ሌሎች ገጣሚያንም ስራዎቻቸውን አቅርበዋል፡፡ በእለቱ ገጣሚ ትዕግስት ስራዎቿን ያቀረበች ሲሆን የታዳሚያን መግቢያ አንድ ሲዲ ነበር፡፡
በሲዲው ውስጥ ከተካተቱት 16 ግጥሞች መካከል “ትዝታና ፍቅር”፣ “ጋዜጠኛው”፣ “ይድረስ ለወንድሜ”፣ “ይማርሽ”፣ “አድዋ”፣ “ክፈለኝ” እና የሲዲው መጠሪያ የሆነው “የእምነት ወጎች” የሚገኙበት ሲሆን በግጥሞቹ ውስጥ ማህበራዊ ጉዳዮች በምፀትና በትዝብት ተዳስሰዋል፡፡ በ50 ብር እየተሸጠ ያለው የግጥም ሲዲው በአሁኑ ሰዓት ከጎጃም በረንዳ ወደ ዮሃንስ በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኘው “ግሬስ” ህንፃ ላይ እየተከፋፈለ ይገኛል፡፡

Read 2720 times