በዕውቁ ጋዜጠኛ፣ ደራሲና የታሪክ ተመራማሪ ጳውሎስ ኞኞ የሕይወት ታሪክ ዙርያ የሚያጠነጥን አዲስ መፅሐፍ ሰሞኑን በገበያ ላይ ዋለ፡፡
ጳውሎስ ከዚህ ዓለም በሞት ከተለየ 22 ዓመታት በኋላ በጋዜጠኛ ደረጀ ትዕዛዙ የተዘጋጀው ይኸው መጽሐፍ፤ በ308 ገፆች የተቀነበበ ሲሆነ በዘጠኝ ምዕራፎች የተከፋፈለና በበርካታ መረጃዎች የተጠናቀረ ነው፡፡
ከአራተኛ ክፍል የዘለለ የመደበኛ ትምህርት ያልነበረው ጳውሎስ፤ ዝነኝነት ለመቀዳጀት ያበቁትን በርካታ ስራዎች ለማከናወን መቻሉ የህይወት ታሪኩን ለማሰናዳት እንዳነሳሳው አዘጋጁ አስረድቷል፡፡ በአርቲስቲክ ማተሚያ ቤት የታተመው መጽሐፉ፤ በ84 ብር እየተሸጠ ይገኛል፡፡
Saturday, 19 July 2014 12:50
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና