Saturday, 19 July 2014 12:49

የኢትዮጵያ ፊልሞች የተጋፈጡትን ፈተና የሚያሳይ ዘጋቢ ፊልም ይመረቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(2 votes)

          ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከፊልም ባለቤቶች ፈቃድ ውጭ በየድረ-ገፃቸው የኢትዮጵያ ፊልሞችን በማሰራጨት ህገወጥ ገቢ የሚሰበስቡ ወገኖችን የሚያወግዝና ፊልሞቹ የተጋረጠባቸውን ፈተና የሚያሳይ ዘጋቢ ፊልም፤ በዮናታን አበራ አድቨርታይዚንግ የተዘጋጀ ሲሆን የፊታችን ሰኞ በድሪም ላይነር ኢንተርናሽናል ሆቴል ከቀኑ 10፡30 ጀምሮ ይመረቃል ተብሏል፡፡  በአማርኛ ፊልሞች ላይ እየተሰራ ያለው ወንጀል የጋራ ጩኸት ስለሚፈልግ በዘጋቢ ፊልሙ ላይ የተለያዩ የፊልም ባለሙያዎች እንደተሳተፉበት ዮናታን አበራ አድቨርታይዚንግ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡
ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉ የድረ ገፅ ባለቤቶች፣ በፊልሙ ላይ እየሰሩ ያሉት ስራ ህገ-ወጥና የአማርኛ ፊልሞችን ከጨዋታ የሚያስወጣ በመሆኑ፣ ድርጊቱን ለማስቆም የተሰራውን ፊልም ለማሰራጨትና ግንዛቤ ለመፍጠር ከሚመለከታቸው አካላት ድጋፍ የጠየቀው ድርጅቱ፤ ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽ/ቤት እና ከኢትዮጵያ ኦዲዮ ቪዥዋል አሳታሚዎች ማህበር የድጋፍ ደብዳቤ ተሰጥቶታል፡፡ በዘጋቡ ፊልሙ ምረቃ ላይ በኪነ-ጥበብ ሥራ ላይ የተሰማሩ ድርጅቶች፣ የሚመለከታቸው ተቋማትና የመንግስት ባለስልጣናት ይገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል፡፡

Read 1883 times