Print this page
Saturday, 19 July 2014 12:49

የ “ጉማ ፊልም ሽልማት” የዘንድሮ ፊልሞችን እየመዘገበ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በኢትዮ ፊልም ኃ/የተ/የግ/ማህበር አስተባባሪነትና ባለቤትነት የሚዘጋጀው “ጉማ ፊልም ሽልማት” የዘንድሮ ፊልሞችን በሽልማት ውድድሩ ለማካተት ምዝገባ መጀመሩን አስታወቀ፡፡ ለሁለተኛው ዙር የሚወዳደሩ የአምና ፊልሞችን ከመጋቢት 29 እስከ ሚያዚያ 3 በጣይቱ ሆቴል መዝግቦ ማጠናቀቁን የገለፀው ኢትዮ ፊልም፤ በሁለተኛው ዙር ውድድር የዘንድሮዎቹን ለማካተት ከሐምሌ 9 እስከ 16 በጣይቱ ሆቴል ምዝገባ እንደሚያካሂድና ለመመዝገብ ፍላጎት ያላቸው ፊልሞች እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ምዝገባው ከቅዳሜ ከሰዓትና ከእሁድ በስተቀር በስራ ቀናት የሚካሄድ መሆኑንም ድርጅቱ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡

Read 1313 times
Administrator

Latest from Administrator