Saturday, 19 July 2014 12:26

43 ሚ ብር የፈጀው ሆምላንድ ኢንተርናሽናል ሆቴል ዛሬ በባህር ዳር ይመረቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

የቱሪስት መዳረሻ በሆነችው ባህርዳር ከተማ በ43 ሚ. ብር የተገነባው ሆምላንድ ኢንተርናሽናል ሆቴል ዛሬ እንደሚመረቅ የሆቴሉ ባለቤትና ስራ አስኪያጅ አቶ ሙሉጌታ ቢያዝን ለአዲስ አድማስ አስታወቁ፡፡
ሆምላንድ ሆቴል ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ በሶስት ኮከብ ደረጃ አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱን የተናገሩት ባለቤቱ፤ በከፍተኛ ወጪ የማስፋፊያ ስራ እንደተሰራና ወደ አምስት ኮከብ እንዳደገ አስታውቀዋል፡፡ ሆቴሉ 73 ደረጃቸውን የጠበቁ አራት ደረጃ ያላቸው የመኝታ ክፍሎች፣ ከ30-450 ሰዎችን የማስተናገድ አቅም ያላቸው የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ ባርና ሬስቶራንቶች፣ ሰፊ የመኪና ማቆሚያ፣ የሳውና፣ የስቲም ባዝና የማሳጅ አገልግሎቶችን ያሟላ ሲሆን ደረጃውን የጠበቀ የመዋኛ ገንዳውም በቅርቡ ግንባታው ተጠናቆ አገልግሎት እንደሚሰጥ አቶ ሙሉጌታ ተናግረዋል፡፡
ባለአምስት ኮከቡ ሆምላንድ ኢንተርናሽናል ሆቴል፤ ለ153 የአካባቢው ነዋሪዎች የስራ እድል መክፈቱን የተናገሩት ባለቤቱ፤ በኮንፈረንስ ቱሪዝም ቀልብ እየሳበች ላለችው የባህርዳር ከተማ ተጨማሪ ድምቀት እንደሆነም ተናግረዋል፡፡
ሆቴሉ ዛሬ ረፋድ ላይ የክልልና የፌደራል ባለስልጣናት፣ በቱሪዝም ላይ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላት፣ ባለሀብቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በድምቀት እንደሚመረቅ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 2553 times