በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነትና በፆረና ተጋድሎ እውነተኛ ታሪክ ላይ የሚያጠነጥነው “የኢትዮ - ኤርትራ ጦርነትና የፆረና ተጋድሎ” የተሰኘ መፅሀፍ በትላንትናው እለት በሂልተን ሆቴል ተመርቋል፡፡ በምክትል አስር አለቃ የማታወርቅ ተገኝ ተፅፎ በዳዕሮ አድቨርታይዚንግ የተዘጋጀው ይህ መፅሀፍ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት የተከሰቱ ተጋድላችን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል ተብሏል፡፡
በምረቃ ሥነስርአቱ ላይ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ የጦር መኮንኖች፣ የታሪክ ምሁራንና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተው ነበር፡፡