በጋዜጠኛ ኃይለገብርኤል እንደሻው የተዘጋጁ አስራ አንድ ሥራዎች የተካተቱበት የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ በዚህ ሳምንት ለንባብ በቃ፡፡ “ምቀኞች”፣ “ማጅራት መቺዎቹ”፣ “ዳቦ ፍለጋ”፣ “ያን ሰሞን”፣ “እንጀራና ወጥ”፣ “ያላዳፉ ነፍሶች”፣ “አገር ሲያረጅ”፣ “እንመሸከንቱ”፣ “የሸንጎ ዓይን”፣ “ተረኛዋ” እና “አበራ ኩራቴ” የተሰኙ ታሪኮችን የያዘው ባለ 171 ገፅ መፅሐፍ በአሻራ አታሚዎች ኃ.የተ.የግ.ማ የታተመ ሲሆን ዋጋውም 32 ብር ነው፡፡