Saturday, 05 July 2014 00:00

የአባባ ተስፋዬ 91ኛ ዓመት ልደት ዛሬ ይከበራል

Written by 
Rate this item
(5 votes)

በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን “የልጆች ፕሮግራም”  ተረት በማቅረብ ህፃናትን ለረጅም አመታት ያዝናኑትና ያስተማሩት እንዲሁም በተዋናይነታቸው የሚታወቁት አርቲስት ተስፋዬ ሳህሉ (አባባ ተስፋዬ) 91ኛ ዓመት የልደት በዓል ዛሬ ከቀኑ 8፡30 ጀምሮ በእቴጌ ጣይቱ ሆቴል እንደሚከበር ተገለፀ፡፡
የአባባ ተስፋዬን የልደት በዓል ያዘጋጁት ቤተሰቦቻቸውና “ልጆች ኢንተርቴይንመንት” ሲሆኑ አርቲስቶች፣ ታዋቂ ሰዎችና ጋዜጠኞች በሚታደሙበት በዚህ የልደት በዓል ላይ የተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚካሄዱ ተጠቁሟል፡፡

Read 1869 times