Saturday, 05 July 2014 00:00

መፃህፍት አውደ ርዕይና የሚዲያ ኤክስፖ ትላንት ተከፈተ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

አሳታሚዎች፣ መፃሕፍት ሻጮችና መገናኛ ብዙኃን የሚሳተፉበት “ኢትዮ አለም አቀፍ የመፃህፍት አውደ ርዕይ እና የሚዲያ ኤክስፖ” በትላንትናው እለት በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል የተከፈተ ሲሆን ዝግጅቱ እስከ ፊታችን  ሰኞ ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ ታውቋል፡፡
ዝግጅቱ የንባብ ባህል እንዲዳብር፣ የመፃህፍት ገበያ እንዲጎለብት፣ የአሳታሚና የህትመት ኢንዱስትሪው እንዲጠናከር ታልሞ የተሰናዳ እንደሆነ አዘጋጆቹ በላኩት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ “በእውቀትና በመረጃ ለበለፀገ ህብረተሰብ መፃህፍትና ሚዲያ በአንድ ስፍራ” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው አውደ ርዕይና የሚዲያ ኤክስፖ ላይ የተለያዩ አዝናኝ ዝግጅቶች እንደሚቀርቡም ታውቋል፡፡
ትላንትን ጨምሮ ለአምስት ቀናት በሚዘልቀው ዝግጅት ላይ ከ60 በላይ አሳታሚዎች፣ መፃሕፍት ሻጮች፣ የግልና የመንግስት መገናኛ ብዙኃን፣ የጠፉና የማይገኙ መፃሕፍት አቅራቢዎች ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡

Read 1198 times