Saturday, 05 July 2014 00:00

“ሀገርና ፖለቲካ” መፅሀፍ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በሆነው ሀብታሙ አያሌው የተፃፈው “ሀገርና ፖለቲካ” የተሰኘ መፅሀፍ ሰሞኑን  ለንባብ በቃ፡፡ በ18 ምዕራፍና በ272 ገፆች የተቀነበበው መፅሀፉ፤ ስለ ኢትዮጵያ አመሰራረት፣ ስለ ኢትዮጵያ ስያሜ፣ ስለ ፖለቲካና ሃይማኖት፣ ስለ ቀደምት ኢትዮጵያ አፄዎችና ሌሎች በርካታ ርዕሰ ጉዳዮች ተነስተውበታል፡፡ የመፅሀፉ አዘጋጅ አቶ ሃብታሙ አያሌው፤ የኢህአዴግ መንግስት ለታሪክና ለሀገር ያለው እጅግ የመረረ ጥላቻና አፍራሽ ተልዕኮ መፅሀፉን ለመፃፍ እንዳነሳሳው በመግቢያው ላይ ገልጿል፡፡ መፅሀፉ በ54 ብር ከ99 ሳንቲም እየተሸጠ ነው፡፡

Read 1536 times