Saturday, 05 July 2014 00:00

“የሞግዚቷ ልጆች” ፊልም ነገ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በደራሲ ዮሀንስ ፀጋዬና አብዲሳ ምትኩ ተፅፎ በስንታየሁ አባይ የተዘጋጀው “የሞግዚት ልጆች” ፊልም ነገ ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ጀምሮ በሁሉም ሲኒማ ቤቶች ለእይታ ይቀርባል፡፡ በያሬድ ፊልም ፕሮዳክሽን ፕሮዲዩሰርነት የቀረበው ይሄው ፊልም፤ የ1፡45 ሰዓት ርዝመት ያለው ሲሆን የሮማንስ ኮሜዲ ዘውግ እንዳለውም ለማወቅ ተችሏል፡፡
በፊልሙ ላይ አርቲስት አዳነች ወ/ገብርኤል፣ ታሪኩ ብርሀኑ (ባባ)፣ ሚካኤል ጆርጅ፣ ምህረት አበበና ሌሎችም ተዋንያን ተሳትፈውበታል፡፡ የፊልሙ አቅራቢ ያሬድ ፊልም ፕሮዳክሽን ከዚህ ቀደም “ክስተት” እና “አሜን” የተሰኙ ፊልሞችን ማቅረቡ ይታወቃል፡፡

Read 2197 times