Tuesday, 08 July 2014 08:23

“ሰኔ 30 የንባብ ቀን” ነገ ይከበራል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ነገ “ሰኔ 30 የንባብ ቀን” በሚል መሪ ቃል ልዩ ፕሮግራም ያካሄዳል፡፡ የፕሮግራሙ አላማ በንባብ ላይ አገር አቀፍ መነሳሳትን መፍጠር መሆኑን የገለፀው ማህበሩ፤ ፕሮግራሙ ነገ ከጠዋቱ 4 ሰዓት ጀምሮ መነሻውን አራት ኪሎ አደባባይ፣  መድረሻውን አምስት ኪሎ ቴክኖሎጂ ፋኪልቲ የሚያደርግ የእግር ጉዞ እንደሚያካትት አስታውቋል፡፡
በእግር ጉዞው ላይ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር አባላት፣ የመንግስት ተወካዮች፣ የተለያዩ ድርጅቶች ሰራተኞች፣ የኢትዮጵያ ስካውት ማህበር አባላትና ሌሎችም የሚሳተፉ ሲሆን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ካሳ ተክለብርሃንና የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሙሉጌታ ሰኢድ በክብር እንግድነት ተገኝተው ንግግር ያደርጋሉ ተብሏል፡፡ የዝግጅቱ ዋነኛ አላማ ሰኔ 30ን የንባብ ቀን አድርጎ ለመሰየም እና አገር አቀፍ የንባብ መነቃቃትን ለመፍጠር እንደሆነ ከማህበሩ መግለጫ ለማወቅ ተችሏል፡፡  

Read 1837 times