Tuesday, 08 July 2014 08:04

አዳዲስ የሩሲያ ቮድካዎች ለኢትዮጵያ ገበያ ቀረቡ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

አንድ የሩሲያ ባለሃብት ወደ ኢትዮጵያ ያስገቧቸው ሶስት አይነት ቮድካዎች በትላንትናው ምሽት በሂልተን ሆቴል ለትውውቅ ቀረቡ፡፡ የቮድካዎቹን ትውውቅ የማስተባበር ኃላፊነት የወሰደው የሩሲያ የሳይንስና የባህል ማዕከል ሲሆን ሶስቱ ቮድካዎች ፎርቲ ዲግሪ፣ ኢምፔሪያል እና ጎልድ በመባል ይታወቃሉ፡፡ ማዕከሉ በስነ ፅሁፍ፣ በስዕል፣ በሙዚቃ፣ በቱሪዝም፣ በባህልና በሳይንስ ዙሪያ ከተለያዩ ተቋማትና ማህበራት ጋር በሚያዘጋጃቸው ፕሮግራሞች የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ ጎን ለጎን በሁለቱ አገራት የሚደረጉ የንግድ እና የቱሪዝም ትስስሮችን ለማበረታታት የቮድካዎቹን የትውውቅ ፕሮግራም ማስተባበሩን ገልጿል፡፡
“Three Brothers from one River” በሚል የማስታወቂያ መርህ በትላንትናው ምሽት ለትውውቅ የበቁት ቮድካዎች አንድ የሩሲያ ባለሀብት
“ሊኩየር ላክ ኢምፖርተር ፒኤልሲ” በተባለው ኩባንያቸው በኩል ወደ ኢትዮጵያ ያስገቧቸው ናቸው፡፡
በትውውቅ ፕሮግራሙ ላይ በሩሲያ እውቅናና ተወዳጅነትን ያተረፉ የሙዚቃ ቡድን አባላት፣ የሩሲያን ባህላዊና ዘመናዊ ዳንሶችንና ተወዳጅ ዘፈኖቻቸውን በማቅረብ ታዳሚዎችን አዝናንተዋል፡፡

Read 1834 times