በደርግ ዘመን ጠ/ሚኒስትር የነበሩት ፍቅረሥላሴ ወግደረስ “እኛ እና አብዮቱ” በሚል ርዕስ በፃፉት መፅሃፍ ላይ ነገ ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በብሔራዊ ቤተ-መፃህፍትና ቤተ-መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት እንደሚካሄድ ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ አስታወቀ።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሥነ ፅሑፍ ባለሙያ የሆኑት አቶ ሰለሞን ተሰማ ለውይይቱ መነሻ ሃሳብ እንደሚያቀርቡ ሚዩዚክ ሜይዴይ ጠቁሞ፤ የሥነ-ፅሁፍ ቤተሰቦች በውይይቱ ላይ እንዲገኙ ጋብዟል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና