Print this page
Saturday, 21 June 2014 15:05

ዩኒቲ ዩኒቨርስቲ የሚያካሂደው የጥናትና ምርምር ጉባኤ ዛሬ ይጠናቀቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ዩኒቲ ዩኒቨርስቲ ዓመታዊ የጥናትና ምርምር ጉባኤውን በትላንትናው ዕለት የጀመረ ሲሆን፤ ዛሬ እንደሚጠናቀቅ ለማወቅ ተችሏል፡፡ መቻሬ ሜዳ በሚገኘው ሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ኮርፖሬት ሴንተር የሚካሄደው ይሄው ጉባኤ፤ ዘንድሮ ለ13ኛ ጊዜ እየተካሄደ ሲሆን በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የሚሰሩ ምሁራንና የምርምር ተቋማት የሰሯቸው የተመረጡ የጥናትና ምርምር ውጤቶች ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሏል፡፡ በየአመቱ የሚካሄደው ይሄው “Multidisciplinary Research Conference” በትላንትናው እለት ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ተጀምሮ በተለያዩ ምሁራን እየቀረበ ሲሆን የምርምር ውጤቶቹም የማህበረሰቡን ችግር በመፍታትና በማቃለል ረገድ ጉልህ ሚና ይኖራቸዋል ተብሏል፡፡

Read 1420 times
Administrator

Latest from Administrator