የኢትዮጵያን ፊልም 50ኛ ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ በኢዮሃ ሲኒማና በባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የተዘጋጀው የፊልም ስልጠና ረቡዕ ተጠናቀቀ፡፡ ስልጠናው የተሰጠው ወደ 60 ለሚጠጉ የፊልም ባለሙያዎችና ጋዜጠኞች ሲሆን በፊልም መመሪያና ስነ ምግባር፤ በፊልም ዝግጅት፣ በፊልም ስክሪፕት አፃፃፍና በፊልም ትወና ላይ ያተኮረ እንደነበር በማጠናቀቂያው ላይ ተገልጿል፡፡
ለአራት ቀናት በቆየው በዚህ ስልጠና ላይ ዮናስ ብርሃነ መዋ፣ ብርሃኑ ሽብሩ፣ ሄኖክ አየለ እና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመጡ የስነ ልቦና ባለሙያዎች በአሰልጣኝነት መሳተፋቸውም ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና