“ልቡን በላው”... ፈሊጣዊ አነጋገር እንዳይመስላችሁ። በደቡብ አፍሪካ የኬፕታውን ነዋሪ የሆነው የዚምባብዌ ተወላጅ እንደ አውሬ ነው፤ የባላንጣውን ልብ ሲበላ የተገኘው። አስደንጋጩ ወንጀል የተፈፀመው በቀድሞ ፍቅረኛው ቤት ውስጥ ነው።
የፀብ ምልክት አልነበረም ብላለች የቀድሞ ፍቅረኛው። ከተለያዩ ቆይተዋል። በድብቅ የተደረገ ነገር የለም። ከሱ ተለይታ ከ62 አመት አዛውንት ጋር መኖር ጀምራለች። ባለፈው ረቡዕ እለት የቀድሞ ፍቅረኛዋ ቤቷ ድረስ ሲመጣ፤ ክፉ ነገር እንዳልጠረጠረች ገልፃ፤ መጠጥ ገዝቼ እንዳመጣ ገንዘብ ሰጥቶኛል ብላለች።
አፍታ አልቆየችም። መጠጥ ገዝታ ስትመጣ፤ ቤቱ ደም በደም ሆኗል። የ62 ዓመቱ አዛውንት በቀድሞ ፍቅረኛዋ ተወግተው ሞተዋል። አንገታቸው በስለት ቆስሏል። ፊታቸው ተነክሷል፤ በጥርስ ተቦጭቋል። ጩኸት ሰምተው የመጡ ጎረቤቶች ወደ ቤት መግባት እንዳልቻሉና በመስኮት ለማየት እንደሞከሩ ጠቅሰው፤ የአዛውንቱን ሆድ ቀድዶ ልባቸው ቆርጦ ሲበላ አይተናል ብለዋል። በድንጋጤ የተደናበሩት ጎረቤቶች ፖሊስ ከጠሩ በኋላ ነው ወንጀለኛው የተያዘው።
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል