Saturday, 14 June 2014 12:28

“Love and Peace” የተሰኘ መፅሀፍ ሊመረቅ ነው የስዕል ኤግዚቢሽን ይከፈታል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

በሰዓሊና ረዳት ፕሮፌሰር ጌታቸው ዮሴፍ ህይወት ዙሪያ የሚያጠነጥነው “Love and Peace” መፅሀፍ የፊታችን ሐሙስ ከቀኑ በ9 ሰዓት በካፒታል ሆቴል ይመረቃል፡፡ በ72 ገፆች የተቀነበበው መፅሐፍ፤ በ150 ብር ለገበያ ይቀርባል ተብሏል፡፡ የተባባሪ ፕሮፌሰሩን የህይወት ታሪክ ፍንትው አድርጎ እንደሚገልፅ የተነገረለት መፅሀፉ፤ በስዊዘርላንዳዊቷ ኤልዛቤት ቢያሲዮ እና በአቶ ዮናስ ታረቀኝ የተዘጋጀ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል፡፡
በሌላ በኩል የተባባሪ ፕሮፌሰር ጌታቸው ዮሴፍ አዳዲስ የስዕል ስራዎች የሚቀርቡበት የስዕል ኤግዚቢሽን በመጪው ማክሰኞ በላፍቶ አርት ጋለሪ የሚከፈት ሲሆን ለአንድ ወር ለተመልካች ክፍት ሆኖ እንደሚቆይም ተጠቁሟል፡፡    

Read 1445 times