Print this page
Saturday, 14 June 2014 12:11

ኤልጂ ሆፕ የሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ በመጪው ዓመት ሥራ ይጀምራል

Written by  መንግሥቱ አበበ
Rate this item
(1 Vote)

         የኮሪያው ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ)፣ ኤልጂ እና ዎርልድ ቱጌዘር የተባሉ ድርጅቶች፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር የፈጠራ ማዕከል ለማቋቋም በትጋት እየሰሩ መሆኑን አማካሪው ኮሚቴ አስታወቀ፡፡
የሕግ፣ የአስተዳደር፣ የሥልጠና ትብብር፣ የተማሪዎች አያያዝና የስትራቴጂክ ፕላን መመሪያዎች ተዘጋጅተው በግምገማ ሂደት ላይ መሆናቸውን የጠቀሰው ኮሚቴው፤ ጎን ለጎን የኮሌጅ ሕንፃ ግንባታም እየተካሄደና በመጪው መስከረም ወር መጨረሻ እንደሚጠናቀቅ ገልጿል፡፡
የኤልጂ ከፍተኛ የአመራር ቡድን፣ ከከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት፣ በስራው ከተሰማሩ ድርጅቶችና ከኢንዱስትሪው ባገኘው አስተያየትና ሐሳብ መሰረት፣ በየትም ቦታ እንደ ሞዴል ሊታይ የሚችል ኮሌጅ ማቋቋም ጠቀሜታው ከፍተኛ እንደሆነ መገንዘቡ ታውቋል፡፡
በሰንዳፋ ወረዳ የሚቋቋመው ኤልጂ ሆፕ መንደር፣ ዓላማው የተሻሻሉ ፕሮግራሞችን በመጠቀም፣ በሶስት ዓመት ውስጥ አካባቢውን ማሳደግ ለማህበረሰቡ አስፈላጊ የሆኑ የመሰረተ ልማት ሕንፃዎችን መገንባትና ራሱን በቋሚነት ማስተዳደር የሚችል የእርሻ መንደር መፍጠር ነው፡፡
እንዲሁም በዚሁ ስፍራ በኢትዮጵያ የሥራ እድል በመፍር ኢኮኖሚውን ለማሳደግ በኮይካ አማካይነት የሚቋቋመው የሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት፣ የኤል ጂ ባለሙያዎች የተጠበቡበትን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ ወደፊት በሙያ የተካኑ ኢንጂነሮችን ለመፍጠርና ለኮሪያ ዘማች ቤተሰቦች ነፃ የትምህርት ዕድል ለመስጠት እንደሚተጋ ታውቋል፡፡
በኤልጂና በኮይካ አማካይነት የሚሰራው የሦስት ዓመት ዕቅድ ኤልጂ የተካነባቸውን መሰረታዊ የኢንፎርሜሽ ቴክኖሎጂ ኮርሶች በማስተማር፣ በየዓመቱ 75 ባለሙያ ኢንጂነሮችን በኤሌክትሮኒክስና በሞባይል ስልክ ያስመርቃል ተብሏል፡፡
ወጣቶቹ በቤትና በቢሮ፣ የኤሌክትሮኒክ ኮሙኒኬሽንና መልቲ ሚዲያ ቁሳቁሶችና ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ የሚሰለጥኑ ሲሆን፣ በሦስቱም የሙያ መስክ 25፣ በአጠቃላይ 75 ወጣቶች ይመረቃሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ለተማሪዎቹ ነፃ ምሳ የሚቀርብ ሲሆን፣ እንደ ፈጠራ፣ ጤና፣ የስራ አመራር፣… ያሉ መሰረታዊ የዝንባሌ ሥልጠናዎች በየሳምንቱ ለአንድ ሰዓት ይሰጣቸዋል።
ሰልጣኞቹ 10ኛ ክፍልን ያጠናቀቁና የ10 ክፍል ተማሪ መሆን ያለባቸው ሲሆን እያንዳንዱ ሰልጣኝ 100 ብር መክፈል አለበት፡፡ ከሰልጣኞቹ መካከል 10 በመቶ ያህሉ የኮርያ ዘማቾች ቤተሰብና የመክፈል አቅም የሌላቸው የድሃ ልጆች ሲሆኑ ክፍያው አይመለከታቸውም፡፡  


====================

ወቅታዊ የቢዝነስና ኢኮኖሚ መፃህፍት

The Divide - በማት ታይቢ
Lean in  - በሼሪል ሳንድበርግ
Thrive  - በአሪያና ሃፊንግተን
The Confidence code - በካቲ ካይና ክሌይር ሺፕማን
Think like a Freak - በስቲቨን ዲ.ሌቪትና ስቲፈን ጂዱብነር
David and Goliath - በማልኮልም ግላድዌል
Creativity, Inc.  - በኢዲ ካትሙል
Capitalist in the Twenty First Century    -  በቶማስ ፒኬቲ
Stress Test - በቲሞቲ ጌይትነር
The Wolf of wall Street - በጆርዳን ቤልፎርት
Flash Boys - በማይክል ልዊስ
(Forbes መፅሄት ሰሞኑን ባወጣው ዕትሙ እነዚህን የመፃህፍት ዝርዝር የንባብ አማራጮች አድርጎ አቅርቧቸዋል)

Read 2000 times