Saturday, 07 June 2014 14:30

ጉጉል ሹፌር አልባ መኪኖችን ይሰራል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ዋና ስራ - የኢንተርኔት አገልግሎት፣ ሶፍትዌር እና የቴሌኮም ምርት
በአመት የ60 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው አገልግሎቶችንና ምርቶችን ይሸጣል
ባለፈው አመት 13 ቢ. ዶላር አትርፏል
የኩባንያው ሃብት 120 ቢ. ዶላር ገደማ ነው
50ሺ ሰራተኞች አሉት
በኢንተርኔቱ አለም ቀዳሚ ስፍራ ይዟል
አስር የሚሆኑ ቶዮታ፣ አውዲ እና ሌክሰስ መኪኖች ያለ አሽከርካሪ እንዲቀሳቀሱ  ለማድረግ በተራቀቁ ቴክኖሎጂዎች ሙከራ ሲያካሂድ የከረመው ጉጉል፣ ከመቶ እስከ ሁለት መቶ የሚደርሱ የራሱ አዳዲስ መኪኖችን በመፈብረክ ለገበያ እንደሚያቀርብ ገልጿል። ጉጉል ሙከራውን ያካሄደው፣ ሁለት የአሜሪካ ግዛቶች (ኔቫዳ እና ፍሎሪዳ) በየጎዳናው አሽከርካሪ አልባ መኪኖች እንዲንቀሳቀሱ የሚፈቅድ ህግ ካወጡ በኋላ ነው።
ለሙከራ ያገለገሉት አስር መኪኖች ያለ አሽከርካሪ እንዲንቀሳቀሱ፣ ለእያንዳንዳቸው የ70ሺ ዶላር የራዳር ሲስተምን ጨምር 150ሺ ዶላር የሚያወጡ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ተገጥሞላቸዋል። በአመት ውስጥ ለገበያ ይቀርባሉ የተባሉት የጉጉል መኪኖች፣ ቢያንስ ቢያንስ ሰፊ ገበያ እስኪያገኙ ድረስ ዋጋቸው ውድ ሊሆን ይችላል ተብሏል። መሪ አልያም ፍሬን የሚባል ነገር የላቸውም። ማብሪያና ማጥፊያ በመንካት ነው መኪናውን የሚያስነሱት።
በፅሁፍ ወይም በካርታ የት መሄድ እንደሚፈልጉ ሲያሳውቁ፤ መኪናው በራሱ ጊዜ ይንቀሳቀሳል። ለሙከራ የተገጣጠሙት መኪኖች በመቶ ሺ ኪሎሜትር የሚቆጠር መንገድ በከተማና በገጠር ተጉዘዋል፤ አንድም ጊዜ ግጭት አላገጠማቸውም።

Read 3296 times