Saturday, 07 June 2014 14:21

ህፃናት ለእግዚአብሔር የፃፏቸው ደብዳቤዎች

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ውድ እግዚአብሔር፡-
ስቴፕለር ከታላላቅ ፈጠራዎችህ አንዱ ይመስለኛል፡፡
        ሩት
- የ5ዓመት ህፃን

ውድ እግዚአብሔር፡-
ቀናተኛ ዓምላክ ነህ ሲባል ምን ማለት ነው? እኔ እኮ ሁሉ ነገር ያለህ ነበር የሚመስለኝ፡፡
                        ጆን
- የ7 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
የሰንበት ት/ቤት ለምን እሁድ ሆነ? የእረፍት ቀናችን እኮ ነው፡፡
        ራሄል
 - የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
በእናትህ ትንሽዬ ፈረስ ላክልኝ፡፡ ብትፈልግ መዝገብህን ማየት ትችላለህ፡፡ ምንም ጠይቄህ አላውቅም፡፡
                        ብሩስ
- የ 5 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
ምናልባት ቃየንና አቤል የየራሳቸው ክፍል ቢኖራቸው ኖሮ አይገዳደሉም ነበር፡፡
ላሪ
 - የ8 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
አንዳንዴ የፀሎት ጊዜም ባይሆን ስለአንተ አስባለሁ፡፡
ማርሻ - የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
ለአንተ ከሚሰሩልህ ሰዎች ሁሉ የበለጠ የምወዳቸው ኖህና ዳዊትን ነው፡፡
ሳሚ
- የ7 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
በመፅሃፍ ቅዱስ ላይ እንዳለው ሰውዬ 900 ዓመት መኖር እፈልጋለሁ፡፡ እወድሃለሁ እሺ፡፡
ዶን
- የ6 ዓመት ህፃን

Read 1383 times