በዶ/ር መልካሙ ታደሰ የተዘጋጀው “የጐጆ ድርጅት” (Home business) የተሰኘ መጽሐፍ ዛሬ ከቀኑ በ8 ሰዓት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የባህል ማዕከል ይመረቃል፡፡ መጽሐፉ በዋናነት ዜጐች እውቀታቸውን፣ ችሎታቸውን እንዲሁም ትርፍ ጊዜያቸውን በመጠቀም ከመኖሪያ ቤታቸው ተጨማሪ ገቢ በማግኘት፣ ራሳቸውንና አገራቸውን ተጠቃሚ የሚያደርጉበትን መንገድ ያመላክታል ተብሏል፡፡ በምረቃው ላይ በመጽሐፉ ዙሪያ ውይይት እንደሚደረግ ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና