ሚድሮክ ኢትዮጵያ የአትሌቲክስ ክለብ ይመሠረታል
ሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ በሚቀጥለው ዓመት የአትሌቲክስ ስፖርት ክለብ እንደሚመሰርት አስታወቀ፡፡ በሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ስር ባሉ ኩባንያዎች መካከል ዘንድሮ ለ11ኛ ጊዜ የተካሄደው ዓመታዊ የስፖርት ውድድር ሰሞኑን ተጠናቅቋል፡፡ በዚሁ ዓመታዊ የስፖርት ውድድር መዝጊያ ስነስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት ዋና ስራ አስፈፃሚው ዶ/ር አረጋ ይርዳው የሚድሮክ ኢትዮጵያ የአትሌቲክስ ክለብ ለመመስረት የተወሰነው በስፖርቱ እድገት ላይ ተገቢውን ድርሻ ለማበርከት ታቅዶ ነው ብለዋል፡፡ የመቻሬ የእግር ኳስ ክለብ ወደ ብሔራዊ ሊግ ደረጃ ለማድረስ ከፍተኛ ጥረት እንደሚያደርግም ዋና ስራ አስፈፃሚው ተናግረዋል።
Published in
ስፖርት አድማስ