Saturday, 24 May 2014 15:09

“ከሰላምታ ጋር” መታየት ሊጀምር ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በደራሲ መዓዛ ወርቁ “Desperate to Fight” በሚል በእንግሊዘኛ ቋንቋ ተፅፎ በሱንዳንስ ተቋም የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ውድድር ላይ የተመረጠው ተውኔት፤ “ከሰላምታ ጋር” በሚል ርዕስ ወደ አማርኛ ተተርጉሞ በኢትዮጵያ መታየት ሊጀምር ነው፡፡ ቲያትሩ ከዚህ ቀደም በእንግሊዝኛ ቋንቋ በኬንያ፣ በኒውዮርክ፣ በስቶክሆልም ስዊድን ለተመልካች ቀርቦ ተወዳጅነትን እንዳተረፈ ተገልጿል፡፡ በተጨማሪም በጀርመንኛ ቋንቋ ተተርጎሞ በጀርመን እና በአውሮፓ ለሚገኙ ተመልካቾች ለማቅረብ theatralize company ከደራሲዋ ጋር ኮንትራት ተፈራርሟል፡፡ ቲያትሩ የኬኒያ፣ የዩጋንዳ፣ የአሜሪካ እና የስዊድን ዜግነት ባላቸው ተዋንያን የተሰራ ሲሆን ለሀገራችን በሚቀርበው ተውኔት ላይ በቲያትር ሙያ የዳበረ ዕውቀት እና ልምድ ያላቸው አርቲስት ኤልሳቤጥ መላኩ እና ፈለቀ የማርውሃ አበበ እንደሚተውኑበት ታውቋል፡፡
በኪባ መልቲ ሚዲያ ፕሮዳክሽን ፕሮዱዩስ የተደረገው ይኸው ቲያትር፤ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ በጃዝ አምባ ላውንጅ በየሳምንቱ ለተመልካች ይቀርባል ተብሏል፡፡ ወደፊትም በሌሎች መድረኮች እንደሚቀርብ ለማወቅ ተችሏል፡፡   

Read 1801 times