Saturday, 24 May 2014 15:02

ህፃናት ለእግዚአብሔር የፃፏቸው ደብዳቤዎች

Written by 
Rate this item
(4 votes)

ውድ እግዚአብሔር-
ስለአንተ ሥራ አስተማሪያችን  ነግራናለች፡፡ አንተ እረፍት ስትወጣ ግን  ማነው የሚሰራልህ?
ዴቪድ-የ5 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር-
እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ፡፡ አንተስ?
ቤቢ- የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር-
ትምህርት ቤት ስንማር፣ መብራት የፈጠረው ቶማስ ኤዲሰን ነው ተብለን  ነበር፡፡ ሰንበት ት/ቤት ደግሞ አንተ እንደፈጠርከው ነገሩን፡፡ ኤዲሰን ያንተን ሃሳብ ሰርቆብህ ነው አይደል ?
ዮኒ - የ7 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር-
ህፃን ወንድም ስለሰጠኸኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ እኔ ግን የጠየኩህ የምታምር ቡችላ እንድትሰጠኝ ነበር፡፡
ቤቲ- የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር-
ስለእኔ እንዳታስብ እሺ፡፡ ሁልጊዜ መንገድ ስሻገር ግራና ቀኙን በደንብ አይቼ ነው፡፡
ዳኒ-የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር-
እሁድ እለት ቤተክርስትያን የምትመጣ ከሆነ አዲሱን ጫማዬን አሳይሃለሁ፡፡
ሚኪ-የ5 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር-
በዓይን የማትታየው ሰማይ ሩቅ ስለሆነ ነው አይደል?
ሳሚ- የ4 ዓመት ህፃን

Read 1667 times