Monday, 19 May 2014 08:08

ለደቡብ ሱዳን 5 ፕሬዚዳንቶች ያስፈልጓታል ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ሴንትራል አፍሪካ ለሁለት ከመሰንጠቅ የሚያድናት አልተገኘም

             በአገር ስ ም እ ና ዘ ረኝነት ወ ይም ደ ግሞ በሃይማኖት ሰበብና በአክራሪነት ሳቢያ የሚቃወሱ አገራት እየተበራከቱ፤ በተቃራኒው የመፍትሔ ሃሳቦች እየተመናመኑ መምጣታቸውን ከደቡብ ሱዳንና ከሴንትራል አፍሪካ ትርምስ ማየት ይቻላል። የዘመናችን ነገር! የግጭቱ መነሻ የኢኮኖሚ ችግርና ሙስና፣ የስልጣን ሽኩቻና የምርጫ ውዝግብ ሊሆን ቢችልም፤ ዞሮ ዞሮ ወደ አስፀያፊ ዘረኝነት ወይም ወደ አስቀያሚ አክራሪነት መዝቀጡ የተለመደ ሆኗል። ዩክሬንን አይቶ ደቡብ ሱዳንን፤ ሶሪያን አይቶ ሴንትራል አፍሪካን ማየት ነው። ለሁለቱ አገራት ቀውስ እልባት ለማፈላለግ ደፋ ቀና የሚሉ አልታጡም። ከጐረቤት አገራትና ከአፍሪካ ህብረት ጀምሮ እስከ አሜሪካና አውሮፓ ህብረት፣ እስከ ቻይናና የተባበሩት መንግስታት... ሰላም ለማምጣት ጉድጉድ ያላለ የለም። ነገር ግን እስካሁን ሁነኛ መፍትሔ አልተገኘም።

እናም በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎች ተገድለዋል፤ ሚሊዮኖች ተሰደዋል። በእርግጥ፤ ሰላም ለመፍጠር የሚካሄዱ ሙከራዎች ዋጋ ቢስ ናቸው ማለት አይደለም። ቢያንስ ቢያንስ፤ በአፍሪካ እንደ ድሮው ያለ ከልካይ “አገር በቀል እውቀት” በሚል ሰበብ ስልጣኔን እያንቋሸሸ፤ አልያም የአሜሪካና የአውሮፓ የሳይንስ ትምህርትን እያብጠለጠለ፣ ኋላቀርነትን የሚሰብክ ፕሮፌሰርና ዶክተር ሞልቷል። ቦኮ ሐራም ከዚህ የተለየ አላማ የለውም። ስሙ ራሱ፤ “የምዕራባዊያን ትምህርት ሐራም ነው” እንደማለት ነው። ቦኮ ሐራም፤ ከወገኛ ምሁራን የሚለይበት ዋነኛ ባህርይው፤ ኋላቀርነትን በመስበክ ብቻ የሚመለስ አለመሆኑ ነው። ስብከቱን በተግባር ያሳያል። አዳሪ ትምህርት ቤት ውስጥ ገብቶ ከ50 በላይ ተማሪዎችን መግደል፤ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከልን አቃጥሎ ደርዘኖችን መጨፍጨፍ፣ ሴት ተማሪዎችን መውሰድ... የሳይንስ ትምህርትን ከማንቋሸሽ አልፎ፤ ሳይንስ የሚያስተምሩና የሚማሩ ሰዎችን ያሳድዳል።

ቦኮ ሐራም በሚፈነጭበት ሰሜናዊ የናይጄሪያ አካባቢ፣ “276 ሴት ተማሪዎች መጠለፋቸውን ብቻ ታወራላችሁ። በሦስት እጥፍ የሚበልጡ ተማሪዎችን ጠልፈናል። ሰሞኑን በአንድ ቦታ 300 ሰዎች ገድለናል። ለምን ይሄ አይወራም?” የቦኮ ሐራምና የአቡበከር ቁጣ፡ “የገደልነውና የጠለፍነውን ያህል አልተወራልንም” የሽብር ፍርሃት ስለነገሰ ብዙዎቹ ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። የአመቱ ፈተና እንዳያመልጣቸው በአንድ ትምህርት ቤት ለመሰባሰብ የደፈሩት ሴት ተማሪዎችም፤ ከቦኮ ሐራም አላመለጡም። ትምህርት ቤቱን በመውረር ነው 276 ሴት ተማሪዎችን የጠለፋቸው። ከወላጆችና ከቤተሰቦች እሮሮ ጋር የባኮ ሐራም ዝና በመላው አለም የገነነው፤ ከዚሁ ጠለፋ ጋር ተያይዞ ነው። ተቃውሞና ውግዘት ከየአቅጣጫው ከሁሉም የአለም ማዕዘናት ጐረፈ። የባኮ ሐራም አለቃ ነውጠኛው አቡባከር ባለፈው ሰኞ በቁጣ እየደነፋ ለአለማቀፉ እሪታ ምላሽ ሰጥቷል።

ውግዘት ስላበዛ አይደለም አቡበከር የተናደደው። “ጥፋት አልሰራሁም፤ ጥፋቴ ተጋነነ” የሚል አይደለም የአቡበከር ምላሽ። በተቃራኒው፤ “የሰራሁትን ነገር አሳነሳችሁብኝ” በማለት ቁጣውን የገለፀው አቡባከር፤ ከተወራለት የሚበልጥ ጠለፋና ግድያ እንደፈፀመ ድርጊቶቹን በመዘርዘር ተናግሯል። አለም ሁሉ የሚያወራው ስለተጠለፉት ሴቶች ብቻ መሆኑ አናድዶታል። በአመት ውስጥ በሶስት እጥፍ የሚበልጡ ታዳጊዎችን እንደጠለፍን ለምን ይዘነጋል? አለም ሁሉ ይህንን የ ማ ያ ወ ራ ው ለ ም ን ድ ነ ው ? በማለት ብስጭቱን ገልጿል አቡበከር። የተናደደው በዚህ ብቻ አይደለም። ቦካ ሐራም ሴት ተማሪዎችን ከመጥለፉ በፊትም ሆነ በኋላ የፈፀምኳቸው ብዙ “ጀብዱዎች” ቸል ተብለውብኛል ባይ ነው - አቡበከር። ከወር በፊት በናይጄሪያ ዋና ከተማ በአቡጃ የአውቶብስ መነሃሪያ ላይ ባደረሰው የፍንዳታ ጥቃት 71 ሰዎች ተገድሏል። ይሄስ ለምን ተረሳ? ለምን አይወራም? አቡበከር በዚህ ሁሉ ይንገበገባል። በቅርቡ ከሳምንት በፊትም ቦኮ ሐራም በአንዲት ከተማ መስጊድ ውስጥ የተጠለሉ 300 ሰዎችን ጨፍጭፏል። ይሄም መነጋገሪያ መሆን እንዳለበት አቡበከር አሳስቧል።

እውነትም፤ ቦኮ ሐራም፤ በአማካይ በየእለቱ 10 ናይጀሪያዊያን እየገደለ በሁለት ዓመታት ውስጥ ከሰባት ለደቡብ ሱዳን 5 ፕሬዚዳንቶች ያስፈልጓታል ተባለ ሴንትራል አፍሪካ ለሁለት ከመሰንጠቅ የሚያድናት አልተገኘም እንደልብ እየተዋጉና እየተጨፈጨፉ አመታትን የመቁጠር ልምድ ቀንሷል። በአንድ በኩል የግጭቱ መሪዎች አለማቀፉ የወንጀል ፍ/ቤት ጥርስ ውስጥ እንዳይገቡ ትንሽ ትንሽ ይፈራሉ። በሌላ በኩል፤ ጥላ ከለላ የሚሆንላቸውና “አይዞህ ጨፍጭፍ” እያለ የሚያበረታታ ሃያል አገር በቀላሉ አያገኙም። “ተደራደሩ” እያለ የሚገፋፋና ጫና የሚያሳድር ሲበዛባቸው፤ የሰላም ስምምነት መፈራረማቸው አይቀርም። ግን ምን ዋጋ አለው? ሳምንት ሳይቆይ ግጭቱ ያገረሻል። በሃይማኖትና በዘር የተቧደኑ ነውጠኞችየገነኑበት አስቀያሚ ግጭት ለገላጋይ አስቸጋሪ ሆኗል። አዲስ አበባ መጥተው የሰላም ስምምነት የተፈራረሙ ተቀናቃኞች፤ በማግስቱ ወደ ደቡብ ሱዳን ሲመለሱ ነው የግጭት ዘመቻ የሚጀምሩት። በመሃል፤ ሕይወት ይረግፋል፤ ኑሮ በስደት ይመሳቀላል። አንዲት የደቡብ ሱዳን ከተማ በአንድ ወር ውስጥ ብቻ፣ ተቀናቃኝ ጦሮች በየተራ አንዱ በሌላው ላይ እየዘመቱ፣ አምስት ጊዜ ተፈራርቀውባታል። ታዲያ ዘመቻው በተቀናቃኝ ጦር ላይ ብቻ ያነጣጠረ አይደለም። በውጊያው አሸንፎ ከተማዋን የሚቆጣጠር ጦር፣ የከተማዋ ነዋሪዎች ላይም ይዘምታል - በዘር እየለየ። ደግሞም በድብቅ የሚካሄድ ዘመቻ አይደለም።

የጦር መሪዎች የጭፍጨፋ ዘመቻ የሚያውጁት በሬድዮ ነው። የዘመናችን ግጭቶች መነሻቸውም ምንም ይሁን ምን፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ መልካቸው ይቀየርና፣ የጭፍጨፋ ዘመቻ የሚያውጁ ጨካኝ አረመኔዎችገንነው ይወጣሉ። የአንዱን ጐሳ ተወላጆች በጠላትነት እየፈረጁ “ከተማዋን ለቀው ካልወጡ ከየቤታቸው እየለቀማችሁ ግደሏቸው። ሴቶቹን በሙሉ ድፈሯቸው” እያሉ ይቀሰቅሳሉ። እና የሰላም ስምምነት በተፈራረሙ ማግስት የእልቂት ዘመቻ የሚያውጁ ከሆነ ምን ይሻላል? የአገሪቱ የቀድሞ ባለስልጣናት፤ ታዋቂ የህግ ባለሙያዎችና የፖለቲካ ምሁራን ተሰባስበው ያመጡትን የመፍትሔ ሃሳብ ተመልከቱ። “አሉ የተባሉ” የደቡብ ሱዳን ታላላቅ ሰዎች የመፍትሔ ሃሳባቸውን ሲያቀርቡ፤ በመጀመሪያ አገሪቱ አንድ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ሁለት ምክትሎች እንዲሁም 18 ሚኒስትሮች ያስፈልጓታል በማለት ይጀምራሉ። ለአገሪቱ ቀውስ መነሻ የሆነው የፕሬዚዳንት ቦታስ? “አገሪቱ አምስት ፕሬዚዳንቶች ይኖሯታል። በግማሽ አመት እየተፈራረቁ ስልጣን ይይዛሉ” ብለዋል የደቡብ ሱዳን ታላላቅ ሰዎች። የጨነቀው ብዙ ያወራል! የፕሬዚዳንቶችን ቁጥር በማብዛት፤ የስልጣን ሽኩቻንና ኋላቀር የዘረኝነት ፖለቲካን ማስወገድ ይቻላል እንዴ? የሴንትራል አፍሪካ ቀውስም እንዲሁ መላ የሌለው ሆኗል።

በስልጣን ሹክቻ የተጀመረው ቀውስ፤ ያፈጠጠ ያገጠጠ የሃይማኖት አክራሪነት ነግሶበት ወደ እልቂት ለማምራት ጊዜ አልፈጀበትም። “ሰላም አስከባሪ ሃይል” ቢሰማራም፤ የአፍሪካና የአውሮፓ መንግስታት አገር ለማረጋጋት ተፍተፍ ቢሉም፤ መፍትሔ አላመጡም። እንዲያውም “መፍትሔ ሊገኝ ይችላል” የሚል ተስፋም ርቋቸዋል። በሃይማኖት የተቧደኑ አክራሪዎች የገነኑበት ግጭት ምን መላ አለው? ሙስሊም፣ ክርስቲያን እያሉ የጭፍጨፋ ዘመቻ ያካሂዳሉ። እና ምን ይሻላል? ሙስሊሞችን ወደ ሰሜን፣ ክርስቲያኖችን ደግሞ ወደ ደቡብ አቅጣጫ ማሸሽ ብቻ! ከዚህ ውጭ ለጊዜው መፍትሔ አልተገኘም። ለዘለቄታውም አገሪቱ ለሁለት ከመሰንጠቅ የሚያድናት አልተገኘም - እስካሁን።

Read 1927 times